Luke 15:5
TSK
ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል፤
TSK
Treasury of Scripture Knowledge references in መጽሐፍ ቅዱስ.
ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል፤
የሰባውን ፊሪዳ አምጥታችሁ እረዱት፥ እንብላም ደስም ይበለን፤
ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው፤ ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል። እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ።
በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።
የተስፋ አምላክም በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በተስፋ እንድትበዙ በማመናችሁ ደስታንና ሰላምን ሁሉ ይሙላባችሁ።
መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና፤
ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤
ደስታችሁም እንዲፈጸም ይህን እንጽፍላችኋለን።