የኦርቶዶክስ የእምነት መግለጫ

The Orthodox Creed

በእውነት በአንድ አምላክ፣ ሁሉን በሚችል በእግዚአብሔር አብ፣ ሰማይንና ምድርን፣ የሚታየውንና የማይታየውን ሁሉ በፈጠረ እናምናለን።

በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ፣ በእግዚአብሔር አንድያ ልጅ፣ ከዘመናት ሁሉ በፊት ከአብ በተወለደ፣ ብርሃን ከብርሃን፣ እውነተኛ አምላክ ከእውነተኛ አምላክ፣ የተወለደ እንጂ ያልተፈጠረ፣ ከአብ ጋር በመለኮት አንድ በሆነ፣ ሁሉም በእርሱ በሆነ እናምናለን።

ስለ እኛ ስለ ሰዎችና ስለ ደኅንነታችን ከሰማይ ወረደ፤ ከመንፈስ ቅዱስና ከድንግል ማርያም ሥጋን ነሥቶ ሰው ሆነ።

ስለ እኛ በጴንጤናዊው ጲላጦስ ዘመን ተሰቀለ፣ መከራን ተቀበለና ተቀበረ፤ በቅዱሳት መጻሕፍትም እንደተጻፈ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተነሣ።

ወደ ሰማይ ዐረገ፣ በአብም ቀኝ ተቀመጠ፤ ሕያዋንንና ሙታንን ሊፈርድ ዳግመኛ በክብር ይመጣል፣ ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም።

አዎን፣ በመንፈስ ቅዱስ፣ በሕይወት ሰጪው ጌታ፣ ከአብ በሚሠርጽ፣ ከአብና ከወልድ ጋር በሚሰገድለትና በሚከበር፣ በነቢያትም በተናገረ እናምናለን።

በአንዲት ቅድስት፣ ዓለም አቀፋዊትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን። ለኃጢአት ስርየት አንዲት ጥምቀትን እንመሰክራለን።

የሙታንን ትንሣኤና የሚመጣውን ዘመን ሕይወት እንጠባበቃለን። አሜን።